18. እነርሱ ፈጥነው ይምጡ፤ዐይኖቻችን እንባ እስኪያጐርፉ፣ሽፋሽፍቶቻችንም ውሃ እስኪያመነጩ፣ስለ እኛ ሙሾ ያውርዱልን።
19. እነሆ የዋይታ ድምፅ ከጽዮን ተሰምቶአል፤ እንዲህም ይላል፤‘ምንኛ ወደቅን!ውርደታችንስ እንዴት ታላቅ ነው!ቤቶቻችን ፈራርሰዋልና፤አገራችንን ጥለን እንሂድ።’ ”
20. እናንት ሴቶች ሆይ፤ የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፤ጆሮቻችሁን ከአንደበቱ ለሚወጡት ቃላት ክፈቱ፤ሴቶች ልጆቻችሁን ዋይታ፣አንዳችሁም ሌላውን ሙሾ አስተምሩ።
21. ሞት በመስኮቶቻችን ገብቶአል፤ወደ ምሽጎቻችንም ዘልቆአል፤ሕፃናትን ከየመንገዱ፣ወጣቶችን ከየአደባባዩ ጠራርጎ ወስዶአል።