38. ድርቅ በውሆቿ ላይ መጣ!እነሆ፤ ይደርቃሉ፤ምድሪቱ በፍርሀት በሚሸበሩ አማልክት፣በጣዖትም ብዛት ተሞልታለችና።
39. “ስለዚህ የምድረ በዳ አራዊትና የጅብ መኖሪያ፣የጒጒትም ማደሪያ ትሆናለች፤ከእንግዲህ ወዲህ ማንም አይኖርባትም፤ከትውልድ እስከ ትውልድም የሚቀመጥባት አይገኝም።
40. እግዚአብሔር ሰዶምንና ገሞራን፤በዙሪያቸውም የነበሩትን ከተሞች ያለ ነዋሪ እንዳስቀራቸው”ይላል እግዚአብሔር፤“እንዲሁ ማንም በዚያ አይኖርም፣የሚቀመጥባትም አይገኝም።