ኤርምያስ 5:16-19 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

16. የፍላጻቸው ሰገባ እንደ ተከፈተ መቃብር ነው፤ሁሉም ብርቱ ተዋጊዎች ናቸው።

17. ሰብልህንና ምግብህን ጠራርገው ይበሉብሃል፤ወንዶችና ሴቶች ልጆችህን ይውጣሉ፣በጎችህንና ከብቶችህን ይፈጃሉ፤የወይን ተክሎችህንና የበለስ ዛፎችህን ያወድማሉ፤የታመንህባቸውንም የተመሸጉ ከተሞች፣በሰይፍ ያጠፉአቸዋል።

18. “ይሁን እንጂ፣ በዚያን ዘመን እንኳ” ይላል እግዚአብሔር፤ “ፈጽሜ አላጠፋችሁም።

19. ሕዝቡ፣ ‘እግዚአብሔር አምላካችን ይህን ሁሉ ነገር ለምን አደረገብን?’ ብለው ቢጠይቁ ‘እኔን፣ እንደ ተዋችሁኝና በራሳችሁ ምድር ባዕዳን አማልክትን እንዳገለገላችሁ፣ እንደዚሁ የእናንተ ባልሆነ ምድር ባዕዳንን ታገለግላላችሁ’ ትላቸዋለህ።

ኤርምያስ 5