23. አንቺ፣ ‘በሊባኖስ’ ውስጥ የምትኖሪ፣መኖሪያሽን በዝግባ ዛፍ የሠራሽ ሆይ፤ምጥ እንደ ያዛት ሴት፣መከራ በላይሽ ሲመጣ ጩኸትሽ እንዴት ይሆን!
24. “በሕያውነቴ እምላለሁ”፤ ይላል እግዚአብሔር “የይሁዳ ንጉሥ የኢዮአቄም ልጅ ኢኮንያን የቀኝ እጄ የቀለበት ማኅተም ብትሆን እንኳ ኖሮ፣ አውልቄ እጥልሃለሁ፤
25. ሕይወትህን ለሚሿት፣ ለምትፈራቸው ለባቢሎናውያንና ለባቢሎን ንጉሥ ለናቡከደናፆር አሳልፌ እሰጥሃለሁ።
26. አንተንና የወለደችህን እናትህን ወዳልተወለዳችሁበት ወደ ሌላ አገር ወርውሬ እጥላችኋለሁ፤ በዚያም ትሞታላችሁ።