13. ፈረስ በምድረ በዳ እንደሚያልፍ ሁሉ፣እነርሱንም በጥልቁ ውስጥ አሳልፎ መራቸው፤ስለዚህም አልተሰናከሉም፤
14. ወደ ሸለቆ እንደሚወርድ የከብት መንጋ፣ በእግዚአብሔር መንፈስ ዕረፍት ተሰጣቸው።ሕዝብህን በዚህ ሁኔታ የመራሃቸው፣ስምህን የከበረ ለማድረግ ነው።
15. ከተቀደሰው፣ ከተከበረውና ከፍ ካለው ዙፋንህ፣ከሰማይ ወደ ታች ተመልከት፤ኀይልህና ቅናትህ የት አለ?ገርነትህና ርኅራኄህ ከእኛ ርቀዋል።