7. ኢየሩሳሌምን እስኪያጸናት፣የምድርም ምስጋና እስኪያደርጋት ዕረፍት አትስጡት።
8. እግዚአብሔር በቀኝ እጁ፣በኀያል ክንዱም እንዲህ ሲል ምሎአል፤“ከእንግዲህ እህልሽን፣ለጠላቶችሽ መብል እንዲሆን አልሰጥም፤ከእንግዲህ የደከምሽበትን፣አዲስ የወይን ጠጅ ባዕዳን አይጠጡትም።
9. ነገር ግን መከሩን የሰበሰቡ ይበሉታል፤ እግዚአብሔርንም ያመሰግናሉ፤የወይኑን ፍሬ የለቀሙም በመቅደሴአደባባዮች ይጠጡታል።”
10. ዕለፉ፤ በበሮቹ በኩል ዕለፉ፤ለሕዝቡ መንገድ አዘጋጁ፤አስተካክሉ፤ ጐዳናውን አስተካክሉ፤ድንጋዩን አስወግዱ፤ለመንግሥታትም ምልክት አሳዩ።