3. ነገር ግን የፈርዖን ከለላ ውርደት ይሆንባችኋል፤የግብፅም ጥላ ኀፍረት ያመጣባችኋል።
4. ምንም እንኳ ሹሞች በጣኔዎስ ቢኖሯቸውም፣መልእክተኞቻቸው ሓኔስ ቢደርሱም፣
5. ውርደትና ኀፍረት ብቻ እንጂርዳታም ሆነ ረብ በማያስገኙላቸውምንም ጥቅም በማይሰጧቸው ሰዎች ምክንያትሁሉም ለኀፍረት ይዳረጋሉ።”
6. በኔጌቭ ስላሉት እንስሳት የተነገረ ንግር፤መልእክተኞች ሀብታቸውን በአህያ፣ውድ ዕቃዎቻቸውን በግመል ጭነው፣ተባዕትና እንስት አንበሶች፣መርዘኛና ተወርዋሪ እባቦች በሚኖሩበት፣መከራና ጭንቅ ባለበት ምድር ዐልፈው፣ወደማይጠቅማቸው ወደዚያ ሕዝብ፣
7. ርዳታዋም ፈጽሞ ዋጋ ቢስ ወደ ሆነው ወደ ግብፅ ይሄዳሉ።ስለዚህ ስሟን፣ረዓብ፣ ምንም የማትጠቅም ብዬ እጠራታለሁ።
8. አሁንም ሂድ፤ በሰሌዳ ላይ ጻፍላቸው፤በጥቅልል መጽሐፍ ላይ ክተብላቸው፤ለሚመጡትም ዘመናት፣ለዘላለም ምስክር ይሆናል፤
9. እነዚህም የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ለመስማት የማይፈልጉ፣ዐመፀኛ ሕዝቦችና አታላይ ልጆች ናቸው።