ኢሳይያስ 28:7-12 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

7. እነዚህም በወይን ጠጅ ይንገዳገዳሉ፤በሚያሰክርም መጠጥ ይወላገዳሉ፤ካህናቱና ነቢያቱ በሚያሰክር መጠጥ ተንገደገዱ፤በወይን ጠጅ ነገር ተምታታባቸው፤በሚያሰክር መጠጥ ተወላገዱ፤ራእይ ሲያዩ ይስታሉ፤ፍርድ ሲሰጡም ይሰናከላሉ።

8. የማእድ ገበታቸው ሁሉ በትፋት ተሞልቶአል፤ከትውኪያም የጸዳ ቦታ የለም።

9. እነርሱም እንዲህ ይላሉ፤ “የሚያስተምረው ማንን ነው?መልእክቱን የሚያብራራውስ ለማን ነው?ወተት ለተዉት ሕፃናት?ወይስጡት ለጣሉት?

10. በትእዛዝ ላይ ትእዛዝ፣ በትእዛዝ ላይትእዛዝ፤በደንብ ላይ ደንብ፣ በደንብ ላይ ደንብ፤እዚህ ጥቂት፣ እዚያ ጥቂት ነውና።

11. እንግዲያማ እግዚአብሔር፣በባዕድ ልሳን በእንግዳ ቋንቋ ለዚህ ሕዝብ ይናገራል።

12. እርሱ፣“ይህቺ የዕረፍት ቦታ ናት፤ የደከመው ይረፍ፤ይህቺ የእፎይታ ቦታ ናት” ያለው ለማን ነበር?እነርሱ ግን መስማት አልፈለጉም።

ኢሳይያስ 28