5. “ሌቦች ወደ አንተ ቢመጡ፣ዘራፊዎችም በሌሊት ቢገቡ፣የሚሰርቁት የሚፈልጉትን ያህል ብቻ አይደለምን?ወይን ለቃሚዎች ወደ አንተ ቢመጡ፣ጥቂት ቃርሚያ አይተዉምን?አንተ ግን ምንኛ ጥፋት ይጠብቅሃል!
6. ዔሳው ግን እንዴት ተዘረፈ?የሸሸገውስ ሀብት ምንኛ ተመዘበረ!
7. ወዳጆችህ ሁሉ ወደ ድንበር ይገፉሃል፤ጓደኞችህ ያታልሉሃል፤ ያሸንፉህማል፤እንጀራህን የበሉ ወጥመድ ይዘረጉብሃል፤አንተ ግን አታውቀውም።