መዝሙር 86:16-17 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

16. ወደ እኔ ተመልከት፤ ማረኝም፤ለባሪያህ ኀይልህን ስጥ፤የሴት ባሪያህንም ልጅ አድን።

17. የሚጠሉኝ አይተው ያፍሩ ዘንድ፣የበጎነትህን ምልክት አሳየኝ፤ እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ረድተኸኛልና፤ አጽናንተኸኛልም።

መዝሙር 86