15. ይህች ቀኝ እጅህ የተከላት ቡቃያ፣ለራስህ ያጸደቅሃት ተክል ናት።
16. እርሷም በእሳት ተቃጥላለች፤የግንባርህ ተግሣጽ ያጠፋቸዋል።
17. ለራስህ ባበረታኸው የሰው ልጅ ላይ፣በቀኝ እጅህ ሰው ላይ እጅህ ትሁን።
18. ከእንግዲህ አንተን ትተን ወደ ኋላ አንመለስም፤ሕያዋን አድርገን፤ እኛም ስምህን እንጠራለን።
19. የሰራዊት አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፤ መልሰን፤እንድንም ዘንድ፣ፊትህን አብራልን።