ሕዝቅኤል 31:5-9 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

5. ስለዚህ በደን ካሉት ዛፎች ሁሉ፣እጅግ ከፍ አለ፤ቅርንጫፎቹ በዙ፤ቀንበጦቹ ረዘሙ፤ከውሃውም ብዛት የተነሣ ተስፋፉ።

6. የሰማይ ወፎች ሁሉ፣በቅርንጫፎቹ ላይ ጐጆአቸውን ሠሩ፤የምድር አራዊት ሁሉ፣ከቅርንጫፎቹ ሥር ግልገሎቻቸውን ወለዱ።ታላላቅ መንግሥታትም ሁሉ፣ከጥላው ሥር ኖሩ።

7. ከተንሰራፉት ቅርንጫፎቹ ጋር፣ውበቱ ግሩም ነበር፤ብዙ ውሃ ወዳለበት፣ሥሮቹ ጠልቀው ነበርና።

8. በእግዚአብሔር ገነት ያሉ ዝግባዎች፣ሊወዳደሩት አልቻሉም፤የጥድ ዛፎች፣የእርሱን ቅርንጫፎች አይተካከሉትም፤የአስታ ዛፎችም፣ከእርሱ ቅርንጫፎች ጋር አይወዳደሩም፤በእግዚአብሔር ገነት ያለ ማናቸውም ዛፍ፣በውበት አይደርስበትም።

9. በብዙ ቅርንጫፎች፣ውብ አድርጌ ሠራሁት፤በእግዚአብሔርም የአትክልት ቦታ፣በገነት ያሉትን ዛፎች የሚያስቀና አደረግሁት።

ሕዝቅኤል 31