ሉቃስ 14:5-7 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

5. ደግሞም፣ “ከእናንተ አንዱ፣ ልጁ ወይም በሬው በሰንበት ቀን ጒድጓድ ቢገባበት ፈጥኖ የማያወጣው ማን ነው?” አላቸው።

6. እነርሱም ለዚህ አንዳች መልስ ሊያገኙ አልቻሉም።

7. ኢየሱስ ተጋባዦቹ የክብር ስፍራ ሲመርጡ ተመልክቶ፣ እንዲህ ሲል ይህን ምሳሌ ለእነርሱ ነገራቸው፤

ሉቃስ 14