ሆሴዕ 4:5-10 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

5. ቀንና ሌሊት ትደናበራላችሁ፤ነቢያትም ከእናንተ ጋር ይደናበራሉ፤ስለዚህ እናታችሁን አጠፋታለሁ፤

6. ሕዝቤ ዕውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቶአል።“ዕውቀትን ስለናቃችሁ፣እኔም ካህናት እንዳትሆኑ ናቅኋችሁ፤የአምላካችሁን ሕግ ስለ ረሳችሁ፣እኔም ልጆቻችሁን እረሳለሁ።

7. ካህናት በበዙ ቊጥር፣በእኔ ላይ የሚያደርጉት ኀጢአት በዝቶአል፤ክብራቸውንም በውርደት ለውጠዋል።

8. የሕዝቤ ኀጢአት ለመብል ሆኖላቸዋል፤ርኵሰታቸውንም እጅግ ወደዱ።

9. ካህናትም ከሕዝቡ የተለዩ አይደሉም፤ሁሉንም እንደ መንገዳቸው እቀጣቸዋለሁ፤እንደ ሥራቸውም እከፍላቸዋለሁ።

10. “ይበላሉ ግን አይጠግቡም፤ያመነዝራሉ ግን አይበዙም፤ እግዚአብሔርን በመተው፣ራሳቸውን

ሆሴዕ 4