1 ዜና መዋዕል 11:23-33 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

23. ደግሞም ቁመቱ አምስት ክንድ የሆነ አንድ ግብፃዊ ገደለ፤ ግብፃዊው የሸማኔ መጠቅለያ የመሰለ ጦር በእጁ ቢይዝም፣ በናያስ ግን ቆመጥ ይዞ ገጠመው፤ ከግብፃዊው እጅ ጦሩን ነጥቆ በገዛ ጦሩ ገደለው።

24. የዮዳሄ ልጅ በናያስ የፈጸመው ጀብዱ ይህ ነበር፤ እርሱም እንደ ሦስቱ ኀያላን ዝነኛ ሆነ።

25. ከሠላሳዎቹም ይልቅ የበለጠ ክብር ተጐናጸፈ፤ ይሁን እንጂ ክሦስቱ አንዱ አልነበረም፤ ዳዊትም የክብር ዘቡ አዣዥ አደረገው።

26. ኀያላኑም እነዚህ ነበሩ፤የኢዮአብ ወንድም አሣሄል፣የቤተ ልሔሙ የዱዲ ልጅ ኤልያናን፣

27. ሃሮራዊው ሳሞት፣ፊሎናዊው ሴሌድ፣

28. የቴቊሔ ሰው የሆነው የዒስካ ልጅ፣ዒራስ፣ የዓናቶቱ ሰው አቢዔዜር፣

29. ኩሳታዊው ሴቤካይ፣አሆሃዊው ዔላይ፣

30. ነጦፋዊው ማህራይ፣የነጦፋዊው የበዓና ልጅ ሔሌድ፣

31. ከብንያም ወገን የጊብዓ ሰው የሆነው የሪባይ ልጅ ኤታይ፣ጲርዓቶናዊው በናያስ፣

32. የገዓስ ሸለቆዎች ሰው የሆነው ኡሪ፣ዓረባዊው አቢኤል፣

33. ባሕሩማዊው ዓዝሞት፣ሰዓልቦናዊው ኤሊያሕባ፣

1 ዜና መዋዕል 11