1 ነገሥት 4:2-21 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

2. ዋና ዋናዎቹ ሹማምቱም እነዚህ ነበሩ፤የሳዶቅ ልጅ ዓዛርያስ፣ ካህን፤

3. የሺሻ ልጆች ኤሊሖሬፍናአኪያ፣ ጸሓፊዎች፤የአሒሉድ ልጅ ኢዮሣፍጥ፣ ታሪክ ጸሓፊ፤

4. የዮዳሄ ልጅ በናያስ፣ የሰራዊቱ ዋና አዛዥ፤ሳዶቅና አብያታር፣ ካህናት፤

5. የናታን ልጅ ዓዛርያስ፣ የአውራጃገዦች የበላይ ኀላፊ፤የናታን ልጅ ዛቡድ፣ ካህንና የንጉሡየቅርብ አማካሪ፤

6. አሒሳር፣ የቤተ መንግሥቱ አዛዥ፤የዓብዳ ልጅ አዶኒራም የግዳጅ ሥራተቈጣጣሪ።

7. እንዲሁም ሰሎሞን ለንጉሡና ለንጉሡ ቤት የሚሆነውን ቀለብ ከመላው እስራኤል የሚሰበስቡ ዐሥራ ሁለት የአውራጃ ገዦች ነበሩት፤ እነዚህም እያንዳንዳቸው በዓመት ውስጥ የወር ቀለብ የሚያቀርቡ ነበሩ።

8. ስማቸውም እንደሚከተለው ነው፤ቤንሑር፣ በኰረብታማው በኤፍሬምምድር፤

9. ቤንጼቄር፣ በማቃጽ፣ በሻዓልቢም፣በቤትሳሜስ፣ በኤሎንቤትሐናን፤

10. ቤንሔሴድ፣ በአሩቦት ውስጥየሚገኙት ሰኰትና የኦፌር አገርበሙሉ የእርሱ ነበር፤

11. ቤን አሚናዳብ፤ በናፎትረ ዶር፣እርሱም የሰሎሞንን ልጅ ጣፈትንአግብቶ የነበረ ነው፤

12. የአሒሉድ ልጅ በዓና፣ በታዕናክናበመጊዶ እንዲሁም ከጻርታን ቀጥሎቍልቍል እስከ ኢይዝራኤል ባለውበቤትሳን ሁሉ፣ ከዚያም ዮቅምዓምንተሻግሮ እስከ አቤልምሖላና ድረስ፣

13. ቤንጌበር፣ በገለዓድ ራሞት ከተማእዚያው ገለዓድ ውስጥ የምናሴልጅ የኢያዕር መንደሮች፣ በባሳንምየአርጎብ አውራጃ እንዲሁም በሮቻቸው የናስ መወርወሪያ በሆኑ ሥልሳባለ ቅጥር ታላላቅ ከተሞች፤

14. የዒዶ ልጅ አሒናዳብ፤ በማሃናይም፣

15. አኪማአስ በንፍታሌም፣ እርሱምየሰሎሞንን ልጅ ባስማትን አግብቶየነበረ ነው፤

16. የኩሲ ልጅ በዓና፤ በአሴርና በበዓሎት፣

17. የፋሩዋ ልጅ ኢዮሣፍጥ በይሳኮር፣

18. የኤላ ልጅ ሳሚ በብንያም፣

19. የኡሪ ልጅ ጌበር፤በአሞራውያን ንጉሥ በሴዎን ምድር፣በባሳን ንጉሥ በዐግ አገር፣ እርሱምየአውራጃው ብቸኛ ገዥ ነበር።

20. የይሁዳና የእስራኤል ሕዝቦች ብዛታቸው እንደ ባሕር ዳር አሸዋ ሆነ፤ ይበሉ፣ ይጠጡና ይደሰቱም ነበር።

21. ሰሎሞንም ከወንዙ አንሥቶ እስከ ፍልስጥኤማውያን ምድር፣ ከዚያም እስከ ግብፅ ዳርቻ ያሉትን መንግሥታት ሁሉ ገዛ፤ እነዚህም አገሮች ግብር አመጡለት፤ በሕይወት ዘመኑም ሁሉ ተገዙለት።

1 ነገሥት 4